በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የከተማ ጥናት ኮሌጅ (College of Urban Studies /CUS) በመጀመሪያ ዲግሪ ሊሰጥ ለታቀደው የአካባቢ ጥበቃ ሳይንስ (Environmental Science) መርሐ-ግብር በተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት መሰረት፣ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም የግብአት ማሰባሰቢያ ወርክሾፕ ተካሄደ፡፡
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) እየተካሄዱ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎችን አስመልክቶ ለዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የውይይት መርሀ-ግብር ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም በአባይ አዳራሽ ተደረገ፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ ሁሉም የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ሠራተኞች፣ አመራሮችና እና ሰራተኞች እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፍ አመራሮችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል፡፡
በመርሀ-ግብሩ ላይም በዩኒቨርሲቲው እየተካሄዱ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት በዶ/ንጉስ ታደሰ፣ የተሸሻለው የፕሮጀክት ስራዎች አስተዳደር መመሪያ በዶ/ር አለማየሁ ደበበ፣ የዩኒቨርሲቲው የአምስት ዓመት (2019-2023 ዓ.ም) ስትራቴጂክ ዕቅድ በዶ/ር አምሳሉ በደሞ እንዲሁም የተሸሻለ የአካዳሚክ የአመራር ምልመላና መረጣ መመሪያ በዶ/ር ምስጋናው ክፈለው ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
We're on Social Networks. Follow us & get in touch.
Please do not hesitate to contact us:
International and Public Relations Directorate:
PoBox: 5648